avatar
EthioTube
@ethiotube
25.04.2026 16:46
ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ብልፅግና ፓርቲን በይፋ መቀላቀላቸውን አስታወቁ

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የማኅበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ገዢውን ብልፅግና ፓርቲ በይፋ ተቀላቅለዋል።

ዳንኤል 2013 ዓ.ም. በተደረገው ስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ በግል ተወዳድረው ፓርላማ መግባታቸው ይታወሳል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ጥያቄ የቀረበላቸው የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ

“ለሌሎች ዕድል ለመስጠት" ሲሉ በምርጫው ላለመሳተፍ አቅደው እንደነበር ተናግረዋል። ሆኖም ግን "አሁን ሌሎች ዕድል ማግኘታቸውን ስላረጋገጥኩ የብልጽግና ዕጩ ሆኜ ልወዳደር ነው” ሲሉ ዲያቆን ዳንኤል ለ“ምርጫ 2018 – ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

የብልጽግና ፓርቲን ከመቼ ጀምሮ እንደተቀላቀሉ ጥያቄ ቢቀርብላቸውም መልስ ከመስጠት መቆጠባቸው ተገልጿል።

#Ethiopia #ProsperityParty #DanielKibret #EthiopianElection #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa
2 1.6K

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EthioTube

8.5K
ኢትዪትዩብ፦ ኢትዮጵያዊ። ነፃ። ገለልተኛ።

Follow us on other our social media networks:

Facebook*.com/EthioTube
Twitter.com/EthioTube
Youtube.com/EthioTube
Instagram*.com/EthioTube
* Принадлежит организации Meta, которая признана экстремистской и запрещена на территории РФ
Открыть в Telegram