avatar
EthioTube
@ethiotube
24.04.2026 19:17
የአርቲስት ቴዲ አፍሮ ስቱዲዮ በታጠቁ አካላት ተዘረፈ

"ቴዲ አፍሮ እስካሁን በደኅና ሁኔታ ላይ ይገኛል" ተብሏል

የአርቲስት ቴዎድሮስ ካሣሁን (ቴዲ አፍሮ) የሙዚቃ ስቱዲዮ በታጠቁ አካላት መዘረፉን የጀርመን ድምፅ ሬዲዮ ዘግቧል።

ዘረፋው የተፈፀመው ትላንት ሚያዚያ15/2018
ዓ.ም. ከምሽቱ 3 ሰዓት ገደማ ሲኤምሲ አካባቢ በሚገኘው የአርቲስቱ ስቱዲዮ ውስጥ ነው።

መሣሪያ የታጠቁ እና በተሽከርካሪ የመጡ አካላት የስቱዲዮን ጠባቂዎች በመደብደብ አርቲስቱ ለሙዚቃ ሥራው የሚጠቀምባቸውን ንብረቶች መውሰዳቸውን ዘገባው አመልክቷል።

አርቲስት ቴዎድሮስ ካሣሁን «ኢቶሪካ» የተሰኘው የሙዚቃ አልበሙ ከመውጣቱ በፊት ጀምሮ የሥነልቡና ጫና ሊያደርሱ የሚችሉ ወከባዎች በአካባቢው እየተፈጸሙ ቢሆንም፣ እንቅስቃሴው ቢገታም እስካሁን በደኅና ሁኔታ ላይ እንደሚገኝም ዶቼ ቬለ ከምንጮቼ አገኘሁት ባለው መረጃ ገልጿል።

ቴዲ አዲሱን አልበም ለአድማጮች ካደረሰ በኋላ የቅርብ ወዳጁ እንዲሁም ቃልአቀባዩ እና ምክትል ማናጀሩ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ይታወሳል።

#Ethiopia #EthiopianMusic #TeddyAfro #AddisAbaba #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa
2 1 588

Обсуждение 2

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EthioTube

8.5K
ኢትዪትዩብ፦ ኢትዮጵያዊ። ነፃ። ገለልተኛ።

Follow us on other our social media networks:

Facebook*.com/EthioTube
Twitter.com/EthioTube
Youtube.com/EthioTube
Instagram*.com/EthioTube
* Принадлежит организации Meta, которая признана экстремистской и запрещена на территории РФ
Открыть в Telegram