avatar
EthioTube
@ethiotube
22.04.2026 09:21
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ቴዲ አፍሮን ጠንከር ባለ ቃላት ከወቀሱት በኋላ የአርቲስቱ ባልደረባዎች መታሰራቸው ተሰምቷል

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ባለፈው እሁድ ቴዲ አፍሮን በቁራ መስለው “ቁራ የቆሸሸ ቦታ የሚውል በመጮኽ በማልቀስ አካባቢን የሚበክል ነው” በማለት ጠንከር ባለ ቃላት ከወቀሱት በኋላ የአርቲስቱ ሁለት ባልደረባዎች መታሰራቸው ተሰምቷል።

የቴዲ አፍሮ ምክትል ማናጀርና ቃል አቀባይ ማህሌት ሰለሞን እንዲሁም የቅርብ ወዳጁ ነው የሚባለው የሱፍ ያሲን በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተሰምቷል።

ትላንትት ሚያዚያ 13/2018 ዓ.ም. በቁጥጥር ሥር የዋሉትን የአርቲስቱን ባልደረቦች አስመልክቶ እስካሁን ድረስ የፌደራል ፓሊስ ሆነ የአዲስ አበባ ፓሊስ ያወጡት ይፋዊ መግለጫ የለም።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በኦሮሚያ ክልል የተገነባውን ሐሮ ደንዲ ሎጅ ባስመረቁበት ዕለት "እኛ ንስር ነን ቁራ አይደለንም" ሲሉ አርቲስት ቴዲ አፍሮን መተቸታቸው ይታወሳል። ይህን ንግግራቸውን ተከትሎ የአርቲስቱ አድናቂዎች ከፍተኛ ስጋታቸውን ሲገልፁ ቆይተዋል።

#Ethiopia #TeddyAfro #AbiyAhmed #EthiopianMusic #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa
8 5 1.2K

Обсуждение 8

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EthioTube

8.5K
ኢትዪትዩብ፦ ኢትዮጵያዊ። ነፃ። ገለልተኛ።

Follow us on other our social media networks:

Facebook*.com/EthioTube
Twitter.com/EthioTube
Youtube.com/EthioTube
Instagram*.com/EthioTube
* Принадлежит организации Meta, которая признана экстремистской и запрещена на территории РФ
Открыть в Telegram