avatar
EthioTube
@ethiotube
20.04.2026 20:51
የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር የሆኑት አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የእንጨት አካፋይ ወድቆ ጭንቅላታቸው ላይ ጉዳት ደርሶባቸው እንደነበር ገለፁ

አምባሳደር ሬድዋን፤ ኢትዮጵያ የምታስተናግደውን የኮፕ32 ዓለም አቀፍ ስብሰባ በሚመለከት ‎ብሔራዊ ኮሚቴው ከሰሞኑ ባካሔደው ውይይት ላይ ሲካፈሉ የሚያሳየው ተንቀሳቃሽ ምስል መነጋገሪያ ሆኖ ነበር። ሬድዋን ከግንባራቸው ከፍ ብሎ ጭንቅላታቸው ላይ የሚታይ ጠባሳን ተከትሎ በማህበራዊ ሚዲያ ብዙ አስተያየቶች ሲሰጡ ቆይቷል።

አምባሳደሩ ስላጋጠማቸው ክስተት በፌስቡክ ገፃቸው በሰጡት ማብራሪያ "ከሁለት ሳምንት በፊት በሀገራዊ ጉዳይ የሚመክር ስብሰባ አስተናግደን ለምሳ እንዳረፍን ንፋስ ለመከላከል የተጋረደ የእንጨት አካፋይ
( Partition Wall ) ሚዛን ስቶ ሲወድቅ አናቴ ጋርና ትንሽ ገባ ብሎ አገኘኝ" ብለዋል። በዚህ አደጋ ጭንቅላታቸው ላይ መሰንጠቅ እንዳጋጠመ ተናግረዋል።

"ስንጥቁ መሰፋት ስለነበረበት ሐኪሞች በከፊል[ፀጉሬን] ላጩት። እኔ ደሞ ሙሉውን ቢሆን ይሻላል ብዬ እስከሚደርቅ አነሳሁት። እንደልጅነቴ ተመልጬ ሳየው አልጠላሁትም" በማለት መነጋገሪያ ስለነበረው ገፅታቸው ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ሬድዋን፤ ሕክምናቸውን እዚሁ አዲስ አበባ በሚገኝ አሚን ሆስፒታል መከታተላቸውን ገልፀው ወደ ውጭ ሀገር አልወጣሁም" ሲሉ አስታውቀዋል።

#Ethiopia #RedwanHussain #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa
1 1.4K

Обсуждение 1

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EthioTube

8.5K
ኢትዪትዩብ፦ ኢትዮጵያዊ። ነፃ። ገለልተኛ።

Follow us on other our social media networks:

Facebook*.com/EthioTube
Twitter.com/EthioTube
Youtube.com/EthioTube
Instagram*.com/EthioTube
* Принадлежит организации Meta, которая признана экстремистской и запрещена на территории РФ
Открыть в Telegram