avatar
EthioTube
@ethiotube
14.04.2026 20:42
የፊታችን ሀሙስ የሚለቀቀውን የአርቲስት ቴዲ አፍሮ የሙዚቃ አልበም አስመልክቶ ሊሰጥ የነበረው መግለጫ በመንግስት መታገዱ ተሰምቷል

ዛሬ ማክሰኞ ሚያዝያ 6/2018 ዓ.ም. የአርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁንን (ቴዲ አፍሮ) አዲስ አልበም አስመልክቶ በአርቲስ ቴቪ ሊሰጥ የነበረው ጋዜጣዊ መግለጫ በመንግስት መታገዱ ተሰምቷል።

ቴዲ አፍሮ ኢቶሪካ የተሰኘው አዲሱ አልበም ከነገ ወዲያ በራሱ የዩቲዩብ ቻናል ለአድማጮች እንደሚያቀርብ መነገሩ ይታወሳል።

በዚህ ጉዳይ ላይ ድምጻዊው ከተለያዩ ጋዜጠኞች ጋር የሚያደርገውን መግለጫ በቀጥታ ስርጭት ለማስተላለፍ ከአርትስ ቴሌቪዥን ጋር አስቀድሞ ስምምነት ተፈራርሞ የነበረ ቢሆንም፤ ከመንግሥት በቀረበ እገዳ ምክንያት የቀጥታ ስርጭቱ እንዳይካሔድ ተደርጓል።

የአርትስ ቴሌቪዥን የሣራ ኃላፊዎች ከቴዲ አፍሮ አዲስ አልበም ሥምምነት ጋር በተያያዘ ማብራሪያ እንዲሰጡ በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን መጠየቃቸውን ደግሞ ዋዜማ ዘግባለች።

ዛሬ ረፋዱ ላይ የቴሌቪዥን ጣቢያው ሥራ አስፈፃሚን ጨምሮ ሌሎች የጣቢያው ሥራ ኃላፊዎች በባለሥልጣኑ ዋና መሥሪያ ቤት በመገኘት ስለ ሥምምነቱ ማብራሪያ እንደሰጡ ዘገባው አመላክቷል።

#Ethiopia #TeddyAfro #EthiopianMusic #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa
1 1 1.7K

Обсуждение 1

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EthioTube

8.5K
ኢትዪትዩብ፦ ኢትዮጵያዊ። ነፃ። ገለልተኛ።

Follow us on other our social media networks:

Facebook*.com/EthioTube
Twitter.com/EthioTube
Youtube.com/EthioTube
Instagram*.com/EthioTube
* Принадлежит организации Meta, которая признана экстремистской и запрещена на территории РФ
Открыть в Telegram