avatar
EthioTube
@ethiotube
12.03.2026 21:05
ኢትዮጵያዊው ከአሜሪካ ተባረረ

የአሜሪካ መንግስት ስለ ግለሰቡ የሚከተለውን ብሏል:

"​የወንጀል ድርጊት የፈጸመው ህገ-ወጥ ስደተኛ ሰለሞን ቦጋለ የኢሚግሬሽን ጥቅማጥቅሞች ተከልክሎ በመጨረሻም በመጋቢት 5 (እ.ኤ.አ) በፊኒክስ መኮንኖቻችን አማካኝነት ወደ ኢትዮጵያ ተባሯል።

ይህም የሆነው ግለሰቡ ራሱን በግልፅ የ"ፋኖ" (ደረጃ 3 የሽብር ቡድን ተብሎ የተፈረጀ) አባል አድርጎ የሚገልጽባቸው በርካታ የማህበራዊ ሚዲያ አካውንቶችን አይስ (ICE) ካገኘ በኋላ ነው።

​የቦጋለ የፅሁፍ መልዕክቶች (ፖስቶች) በትግራዋዮች ላይ "የማፅዳት" እርምጃ በመውሰድ ከኢትዮጵያ እንዲጠፉ፣ ስደትና ጥቃት እንዲፈጸምባቸው የሚቀሰቅሱ ነበሩ።

​ከ2003 ጀምሮ በኤች.ኤስ.አይ (HSI) የሚመራው የሰብአዊ መብት ተላላፊዎች እና የጦር ወንጀለኞች ማእከል 1,178 የሚሆኑ የታወቁ ወይም የተጠረጠሩ የሰብአዊ መብት ተላላፊዎችን እና የጦር ወንጀለኞችን ከሀገር አባሯል።"

#Ethiopia #UnitedStates #Fano #EthiopianNews #AmharicNews #Africa #EthioTube
1 2 1.8K

Обсуждение 1

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EthioTube

8.5K
ኢትዪትዩብ፦ ኢትዮጵያዊ። ነፃ። ገለልተኛ።

Follow us on other our social media networks:

Facebook*.com/EthioTube
Twitter.com/EthioTube
Youtube.com/EthioTube
Instagram*.com/EthioTube
* Принадлежит организации Meta, которая признана экстремистской и запрещена на территории РФ
Открыть в Telegram