avatar
EthioTube
@ethiotube
19.02.2026 19:05
ዓለም አቀፉ ክራይስስ ግሩፕ በፌደራል መንግሥት፣ በትግራይ ክልል እና በጎረቤት ሀገር ኤርትራ መካከል ያለው ውጥረት ወደ ደም አፋሳሽ ጦርነት ሊከት ይችላል ሲል አስጠነቀቀ

ዓለም አቀፉ ክራይስስ ግሩፕ በፌደራል መንግሥት፣ በትግራይ ክልል እና በጎረቤት ሀገር ኤርትራ መካከል ያለው ውጥረት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መምጣቱን በመግለጽ በዚህ ምክንያት ደም አፋሳሽ ጦርነት ሊከሰት ይችላል ሲል አስጠንቅቋል። ተቋሙ ባወጣው መግለጫ በተጠቀሱት ሦስት አካላት መካከል ውጊያ ከተነሳ ከሱዳን ጦርነት ጋር ተያይዞ ቀጠናውን ወደለየት ትርምስ እንደሚከተውም ገልጿል።

ክራይስስ ግሩፕ ከዚህ ቀደም በአውሮፓውያኑ 2026 ሊከሰቱ የሚችሉ እና የሚቀጥሉ ሲል 10 ጦርነቶችን ይፋ ባደረገበት ሪፖርት ላይ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ለወራት ያህል እርስ በእርስ ሲወቃቀሱ እና ሲካሰሱ መቆየታቸውን ተናግሮ ነበር። በዚሁ ጉዳይ ላይ በድጋሚ ያወጣው ስጋት እና ማሳሰቢያ የታከለበትን ሪፖርት፤ በ 2013 በትግራይ ክልል በተቀሰቀሰው ጦርነት በመቶሺዎች የሚቆጠሩ ንጹኃን መገደላቸውን አስታውሷል። በዚህ ላይ ሌላ ጦርነት መፈንዳቱ ለሦስቱም ተዋናዮች (ለፌዴራል መንግሥቱ፣ ለትግራይ እና ለኤርትራ) እጅግ አውዳሚ ይሆናል። በማለት አሳስቧል።

ይህ እየጠመቀ ያለው ያለው ግጭት፤ ለሦስት ዓመታትን ካስቆጠረው ከሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት ሊገናኝ እንደሚችል እና ከአፍሪካ ቀንድ ውጪ ያሉ ኃያላን ሀገራትን ወደ ግጭቱ በመሳብ ቀድሞውኑ ያልተረጋጋውን የቀይ ባሕርን ቀጠና ሊያናውጥ ይችላል በማለትም አስጠንቅቋል።

#Ethiopia #Eritrea #Tigray #TPLF #CrisisGroup #ICG #InternationalCrisisGroup #EthiopianNews #AmharicNews #EthioTube #Africa #HornOfAfrica
1 1 2.1K

Обсуждение 1

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EthioTube

8.5K
ኢትዪትዩብ፦ ኢትዮጵያዊ። ነፃ። ገለልተኛ።

Follow us on other our social media networks:

Facebook*.com/EthioTube
Twitter.com/EthioTube
Youtube.com/EthioTube
Instagram*.com/EthioTube
* Принадлежит организации Meta, которая признана экстремистской и запрещена на территории РФ
Открыть в Telegram