avatar
EthioTube
@ethiotube
19.12.2025 23:46
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን የመስከረም የደመወዝ ጭማሪ እስካሁንም አለመፈጸሙን ተናገሩ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን፤ በአዲሱ የደመወዝ ማስተካከያ ጭማሪ መሰረት “የመስከረም ወር ክፍያ አልተፈጸመልንም” ሲሉ በማህበራቸው አማካኝነት ቅሬታ አቀረቡ። የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ በበኩሉ ችግሩ የተፈጠረው በመረጃ ክፍተት ምክንያት ለፌደራል መንግስት የተላከው የገንዘብ መጠን ጥያቄ ከሚፈለገው በማነሱ እንደሆነ ገልጾ፤ ይህንኑ ለመቅረፍ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አስታውቋል።

ለመንግስት ሰራተኞች ከመስከረም ወር ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ የደመወዝ ማሻሻያ እንደሚደረግ የፌደራል መንግስት ያስታወቀው ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ላይ ነበር። ሆኖም የደመወዝ ጭማሪው ደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች እስከ ህዳር ወር ተግባራዊ ሳይደረግ ዘግይቷል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ በህዳር መጀመሪያ ላይ በሰጠው መግለጫ፤ በአዲሱ የደመወዝ ማሻሻያ መሰረት የተደረገው ጭማሪ የመስከረም እና የጥቅምት ወር ውዝፍ ክፍያ ከቀናት በኋላ እንደሚፈጸም አስታውቆ ነበር። የክልሉ መምህራን ማህበር ሰብሳቢ አቶ አማኑኤል ጳውሎስ፤ ቢሮው ይህን መግለጫ ከሰጠ በኋላ የጥቅምት ወር ውዝፍ ክፍያ ለመምህራን ቢፈጸምም የመስከረም ወር ግን በአብዛኛው የክልሉ አካባቢዎች እስካሁን አለመከፈሉን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

ይህን ተከትሎ መምህራን ጥያቄ በማንሳት ላይ መሆናቸውን የገለጹት አቶ አማኑኤል፤ ችግሩ በቀጠለባቸው የክልሉ አካባቢዎች የትምህርት ማቆም አድማ የማድረግ ሙከራዎች እንደነበሩ ገልጸዋል።

#Ethiopia #SouthernEthiopia #EthiopianTeachers #EthiopianNews #AmharicNews #Africa #EthioTube
1 2.5K

Обсуждение 1

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EthioTube

8.5K
ኢትዪትዩብ፦ ኢትዮጵያዊ። ነፃ። ገለልተኛ።

Follow us on other our social media networks:

Facebook*.com/EthioTube
Twitter.com/EthioTube
Youtube.com/EthioTube
Instagram*.com/EthioTube
* Принадлежит организации Meta, которая признана экстремистской и запрещена на территории РФ
Открыть в Telegram