avatar
Ethiopia Check
@ethiopiacheck
10.04.2026 15:35
#FakeAccountAlert በኢሕአፓ ዋና ጸሐፊ ሚስጥረስላሴ ታምራት ስም ከተከፈቱ ሀሰተኛ የፌስቡክ ገጾች እና አካውንቶች እንጠንቀቅ

/ኢትዮጵያ ቼክ/- የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ዋና ጸሐፊ የሆኑትን ሚስጥረስላሴ ታምራትን ስም እና ምስል በመጠቀም የተከፈቱ የፌስቡክ ገጾች እና አካውንቶች የተለያዩ መረጃዎችን እያጋሩ መሆናቸዉን ተመልክተናል።

ኢትዮጵያ ቼክ በጉዳዩ ላይ ባደረገዉ ማጣራት በርከት ያሉ ሀሰተኛ የፌስቡክ ገጾች እና አካውንቶች በዋና ጸሐፊዋ ስም መከፈታቸዉን አረጋግጧል።

በሀሰተኛ የፌስቡክ አካውንቶቹ ከተጋሩ መረጃዎች መካከል 7ኛዉን ሀገራዊ ምርጫ ጋር በተገናኘ ግለሰቦች ላይ ያነጣጠሩ የጥላቻ ንግግሮች ይገኙበታል።

ዋና ጸሐፊዋ ከቀናት በፊት በትክክለኛ የፌስቡክ አካውንታቸው ባጋሩት ጽሁፍ “በስሜ ሀሰተኛ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እየተከፈቱና እኔን የማይገልጹ ጽሁፎች እንዲሁም ፎቶዎች ተቀናብረው እየተለቀቁባቸው መሆኑን ተመልክቻለሁ” ብለዋል።

በተጨማሪም ትክክለኛ አካውንታቸዉ ከ55 ሺህ በላይ ተከታዮች ያሉት ይህ አካውንት እንደሆነ ለኢትዮጵያ ቼክ አረጋግጠዋል፡ https://www.facebook*.com/share/17f9UcAsUC/?mibextid=wwXIfr 

የታዋቂ ግለሰቦችን እና ተቋማትን ስም እና ምስል (አርማ) በመጠቀም የሚከፈቱ ሀሰተኛ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እና አካዉንቶች ለሀሰተኛ እና አሳሳች መረጃዎች ሊያጋልጡን ስለሚችሉ ተገቢዉን ጥንቃቄ እናድርግ።

በተጨማሪም ሀሰተኛ እና ተመሳስለዉ የሚከፈቱ አካውንቶችን፣ ገጾችን እና ቻነሎችን ለመለየት የሚረዱን ጠቋሚ ምልክቶችን ለማየት ይህን በኢትዮጵያ ቼክ የተዘጋጀን አጭር ቪድዮ ይመልከቱ፡ @ethiopiacheck1344

ኢትዮጵያ ቼክ

@EthiopiaCheck
18
👍 5
3.7K
* Принадлежит организации Meta, которая признана экстремистской и запрещена на территории РФ

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

Ethiopia Check

24.9K
ኢትዮጵያ ቼክ በማህበራዊ ሚድያ እና በመደበኛ ሚድያዎች የሚቀርቡ ሀሰተኛ መረጃዎችን በማጣራት ስራዎቹን ለተከታታዮቹ ያቀርባል።
Открыть в Telegram