avatar
Ethiopia Check
@ethiopiacheck
01.10.2025 19:45
አራተኛው የአፍሪካ ፋክትስ ሰሚት (Africa Facts Summit) በሴኔጋል መካሄድ ጀመረ

/ኢትዮጵያ ቼክ/- በአፍሪካ የሚገኙ መረጃ አጣሪ ተቋማትና ኤክስፐርቶችን የሚያሳትፈው አመታዊው የአፍሪካ ፋክትስ ጉባዔ በሴኔጋል ዳካር ከተማ መካሄድ ጀምሯል።

ለአራተኛ ጊዜ እየተካሄደ የሚገኘው ይህ ጉባዔ በአፍሪካ የመረጃ ተአማኒነት እንዲጎለብት የሚደረገው ጥረት አካል ሲሆን የመረጃ ማጣራት (fact checking) ልምድ እንዲስፋፋ እና እንዲጎለብት ምክክሮች የሚደረጉበት እንደሚሆን ይጠበቃል።

የሀሰተኛ መረጃ ዘመቻዎችን መመርመር፣ የሰው ሰራሽ አስተዉሎት (AI) ተፅእኖ፣ የተቀናጁ አሰራር አማራጮች፣ ሀሰተኛ መረጃ በግጭት አከባቢዎች እንዲሁም አካባቢ ሁኔታን ያማከሉ መፍትሄዎች የሚሉት የጉባዔው አበይት አጀንዳዎች ናቸው።

በተጨማሪም በጉባዔው በአፍሪካ የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን በመከላከል ረገድ ያሉ እድሎች እና ፈተናዎችን በተመለከተ ውይይቶች ይደረጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ ጉባዔ በተለያዩ ቋንቋዎች የሚሰሩ መረጃ አጣሪ ተቋማት እና የሚዲያ አጠቃቀም ክህሎት ባለሙያዎች ተሳታፊ ናቸው። ኢትዮጵያ ቼክም በዚህ ጉባዔ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።

በመጨረሻም ጉባዔው ለዉድድር ከቀረቡ የአመቱ የሀሰተኛ መረጃ ማጣራት ስራዎች አሸናፊዎች እውቅና እና ሽልማት በመስጠት እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።

ኢትዮጵያ ቼክ!

@EthiopiaCheck
18
👍 6
1 12.5K

Обсуждение 1

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

Ethiopia Check

24.9K
ኢትዮጵያ ቼክ በማህበራዊ ሚድያ እና በመደበኛ ሚድያዎች የሚቀርቡ ሀሰተኛ መረጃዎችን በማጣራት ስራዎቹን ለተከታታዮቹ ያቀርባል።
Открыть в Telegram