#FakeAccountAlert በአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት የአፍሪካ ዳይሬክተር ስም የተከፈተው የፌስቡክ ገፅ ሀሰተኛ ነው
የአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የአፍሪካ ዳይሬክተር በሆኑት በአቶ አበበ አእምሮ ሥላሴ ስም እና ፎቶ (Profile Picture) የተከፈተ አንድ የፌስቡክ ገፅ ከሰሞኑ በርካታ መልዕክቶችን እያስተላለፈ ይገኛል።
ይህ ከ2,500 በላይ ተከታዮች ያሉት ገፅ አቶ አበበ የሚመሩት ተቋም የተለያዩ የኢንቨስትመንት እድሎችን እንደሚደግፍ በመግለፅ ለተለያዩ ግለሰቦች በመደወል እና የፅሁፍ መልዕክት በመላክ ላይ ይገኛል።
ኢትዮጵያ ቼክ አቶ አበበን በዚህ ዙርያ ያነጋገረ ሲሆን እርሳቸውም ከኤክስ (ትዊተር) ውጪ ፌስቡክ እንደማይጠቀሙ እና የፌስቡክ ገፁም የእርሳቸው እንዳልሆነ አስረድተዋል። ትክክለኛው የኤክስ አካውንታቸው ይህ ነው:
https://x.com/aselassie?t=2d32OlM5ich2aRP5JZDRcg&s=09
ተመሳስለው የሚከፈቱ ሀሰተኛ የማህበራዊ ሚድያ ገፆች፣ አካውንቶች እና ቻናሎች ለመጭበርበር፣ ለጥላቻ ንግግሮች እና ለሀሰተኛ መረጃ ስለሚያጋልጡን የምንከተላቸው ግለሰቦች መሆናቸውን እስከምናረጋግጥ ድረስ ጥንቃቄ አይለየን።
ኢትዮጵያ ቼክ
@EthiopiaCheck
Обсуждение 4
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram