avatar
Ethiopia Check
@ethiopiacheck
27.02.2025 23:35
#FactCheck 'ብሔራዊ ባንክ ለመንግሥት አበድሮ ያልመለሰለት ገንዘብ 92.1 ቢሊዮን ብር ደረሰ' በሚል እየተሰራጨ ያለው ዜና ከዘጠኝ አመት በፊት የተሰራ ዘገባ ነው

ሪፖርተር ጋዜጣ የዛሬ ዘጠኝ አመት ገደማ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለፌዴራል መንግሥት በጀት መሸፈኛ ካበደረው ገንዘብ ውስጥ ያልተመለሰለት 92.1 ቢሊዮን ብር መድረሱን ዘግቦ ነበር።

ጋዜጣው በዘገባው ላይ ባንኩ በቀጥታ ለማዕከላዊ መንግሥት አበድሮ ያልተመለሰለት ገንዘብ 83.2 ቢሊዮን ብር ወይም 90.3 በመቶ ሲሆን፣ ቀሪው 9.7 በመቶ ደግሞ በቦንድ ተበድሮ ያልተመለሰለት መሆኑን ጠቅሶ ነበር።

ይሁንና ይህ የሪፖርተር ዘገባ የታተመበት ጋዜጣ የስክሪን ቅጂ (ስክሪንሾት) ከሰሞኑ በስፋት እየተጋራ ሲሆን መረጃው አዲስ እንደሆነ ተደርጎ እየቀረበ መሆኑን ኢትዮጵያ ቼክ ተመልክቷል።

ይሁንና መረጃው አዲስ ሳይሆን እ.አ.አ በፌብሪዋሪ 21/2016 የወጣ ዜና መሆኑን ማየት ችለናል።

ላለፉት 16 ዓመታት ያለገደብ ከብሔራዊ ባንክ ገንዘብ ሲበደር የነበረው የፌደራል መንግሥት ከአገር ውስጥ ገቢ ከ15 በመቶ የበለጠ ገንዘብ በብድር ማግኘት እንዳይችል የሚገድብ ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከወራት በፊት መቅረቡ ይታወሳል።

ለምክር ቤቱ የቀረበው የብሔራዊ ባንክ ረቂቅ አዋጅ መንግሥት የተበደረውን ገንዘብ በአንድ ዓመት ውስጥ ካልመለሰ ከተቋሙ ሌላ ብድር መውሰድ እንደማይችልም ያስቀመጠ ነው።

ኢትዮጵያ ቼክ

@EthiopiaCheck
👍 28
3
2 8 15.2K

Обсуждение 2

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

Ethiopia Check

24.9K
ኢትዮጵያ ቼክ በማህበራዊ ሚድያ እና በመደበኛ ሚድያዎች የሚቀርቡ ሀሰተኛ መረጃዎችን በማጣራት ስራዎቹን ለተከታታዮቹ ያቀርባል።
Открыть в Telegram