avatar
Ethiopia Check
@ethiopiacheck
31.10.2024 16:51
#MediaMonitoring የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኤርትራ የአየር ክልል እንዳይበር እንደተከለከለ የተሰራጨው መረጃ የተሳሳተ እንደሆነ አየር መንገዱ ለኢትዮጵያ ቼክ ተናገረ

በርካታ የኢትዮጵያ፣ የኤርትራ እና የሶማልያ ኦንላይን ሚድያዎች ኤርትራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኤርትራ የአየር ክልል ውስጥ እንዳይበር መከልከሉን እየዘገቡ ይገኛሉ።

እንደ 'Eritrean Press' ያሉ እነዚህ ሚድያዎች ለዚህ ክስተት አስረጂ ነው ያሉትን ማስረጃ ባያቀርቡም ጉዳዩ አየር መንገዱ በቅርቡ ወደ ኤርትራ እንዳይበር ከመታገዱ ጋር የተያያዘ እንደሆነ አመላክተዋል።

በዚህ ዙርያ ኢትዮጵያ ቼክ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ማብራርያ ጠይቋል።

"አየር መንገዳችን አሁንም በኤርትራ አየር ክልል እየበረረ ነው፣ መረጃው የተሳሳተ ነው" ብለው አንድ ከፍተኛ የአየር መንገዱ ሀላፊ መረጃ ሰጥተውናል።

"በኤርትራ አየር ክልል ለመብረር አሁንም ፈቃድ አለን፣ ይህ ፍቃድ እንደተነሳ ምንም አይነት ከኤርትራ አልደረሰንም" ብለው ያስረዱት ሀላፊው ከበፊቱ የተቀየረ ነገር እንደሌለ ጠቁመዋል።

ይሁንና Flight Radar 24 የተባለው የበረራ መከታተያ ድረ-ገፅ እና መተግበርያ አንዳንድ አውሮፕላን የኤርትራን አየር ክልል በመተው በሱዳን በኩል እየበረሩ እንደሆነ በ X ላይ ምላሽ ሰጥቷል።

ይሁንና በርካታ የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች አየር መንገዱ አሁንም በረራውን በኤርትራ የአየር ክልል እያደረገ እንደሆነ የሚያሳዩ የስክሪን ቅጂዎችን እያጋሩ ይገኛሉ።

ኢትዮጵያ ቼክ

@EthiopiaCheck
👍 20
4
2 7 9.4K

Обсуждение 2

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

Ethiopia Check

24.9K
ኢትዮጵያ ቼክ በማህበራዊ ሚድያ እና በመደበኛ ሚድያዎች የሚቀርቡ ሀሰተኛ መረጃዎችን በማጣራት ስራዎቹን ለተከታታዮቹ ያቀርባል።
Открыть в Telegram