avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
17.05.2026 18:09
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በጎዴ እየተገነባ የሚገኘው በዓመት 3 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን ዩሪያ ማዳበሪያ የማምረት ዐቅም ያለው ፋብሪካ ግንባታ በተያዘለት ዕቅድ መሠረት እየተከናወነ መሆኑን አስታወቁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአሊኮ ዳንጎቴ ጋር በመሆን በጎዴ ሥራው የደረሰበትን ደረጃ የገመገሙ ሲሆን በፕሮጀክቱ ስፍራ የሚታየው የሥራ ሂደቱ ፍጥነት አበረታች መሆኑን ገልጸዋል።

ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ የምግብ ሉዓላዊነት፣ የኢንዱስትሪ እድገት እና በኢኮኖሚ ራስን የመቻል ጥረት ውስጥ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው ኢንቨስትመንት መሆኑንም አስረድተዋል።

የማዳበሪያ ፋብሪካው በሚጠናቀቅበት ወቅት የሀገር ውስጥ የማምረት ዐቅምን ያጎለብታል ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ ከውጭ በሚገባ ማዳበሪያ ላይ ያለውን ጥገኝነት በመቀነስ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አርሶአደሮችን ይደግፋል ብለዋል።

እንዲሁም ለኢንቨስትመንት እና የሥራ ዕድል ፈጠራም አዳዲስ እድሎችን ይከፍታል ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልፀዋል።


#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
3
359

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram