avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
15.05.2026 18:12
በ1 ሺህ 234 ወረዳዎች ስኬታማ የአጀንዳ ማሰባሰብ እና የመለየት ስራ መከናወኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን አስታውቋል።

ኮሚሽኑ ይሄንን ያስታወቀው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት የእስካሁን ተግባራትና ቀጣይ አቅጣጫ የሚገመግም መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት በተካሄደበት ወቅት ሲሆን አካታችና አሳታፊ የሆነ የምክክር ተሳታፊዎች የመለየት ስራ የኢትዮጵያን 93 በመቶ የሸፈነ በ1 ሺህ 234 ወረዳዎች መካሄዱንም ጠቅሷል፡፡

በሌላ በኩል በትግራይ ክልል ምክክሩን ለማድረግ የሚያስችል መድረክ በአዲስ አበባና በመቐለ ከተማ 22 ጊዜ ቢደረግም ባለው ምቹ ያልሆነ ሁኔታ በክልሉ በሚገኙ ወረዳዎች ምክክር ለማድረግ አለመቻሉን የጠቀሰው ኮሚሽኑ ዋናውን የምክክር ጉባኤ ማካሄድና ስምምነት የተደረሰባቸውን ውጤቶችና ምክረ ሀሳቦች ተፈፃሚነት ማመቻቸት ቀጣይ ስራዎቹ መሆናቸውንም ይፋ አድርጓል

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
👍 1
2 622

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram