avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
15.05.2026 14:08
በደቡብ አፍሪካ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሱ ያሉ ችግሮችን በጋራ ለመፍታት ስምምነት ላይ መደረሱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገልጿል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ በህንድ በተጀመረው የብሪክስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ በመሳተፍ ላይ ሲሆኑ ከስብስባው ጎን ለጎን ከደቡብ አፍሪካው የዓለም አቀፍ ግንኙነትና ትብብር ሚኒስትር ሮናልድ ላሞላ ጋር ተወያይተዋል።

ውይይቱ በሀገራቱ የሁለትዮሽ ግንኙነት ላይ ያተኮረ ሲሆን ሚኒስትሮቹ በደቡብ አፍሪካ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሱ ያሉ ችግሮችን በጋራ ለመፍታት መስማማታቸው ተገልጿል።
 
ሚኒስትሩ ከዚሁ ስብሰባ ጎን ለጎን ከህንድ አቻቸው ጋር ተወያይተው የሁለቱን ሀገራት የረጅም ጊዜ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር በጋራ ጉዳዮች ላይ በትብብር መስራት አስፈላጊ መሆኑን ተማምነናል ብለዋል።

የህንዱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በበኩላቸው ሀገራቸው የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ይበልጥ ለማጠናከርና በተለያዩ ዘርፎች በጋራ ለመስራት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላት ጠቁመዋል፡፡

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
452

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram