avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
15.05.2026 14:02
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ትራምፕ የቻይናው አቻቸው ሺ ጂንፒንግ ኢራን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ እንዳይኖራት በሚለው ውሳኔ መስማማታቸውን ገለፁ።

ፕሬዝዳንት ትራምፕ በቻይና ያደረጉትን የ2 ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ዛሬ አጠናቀው ወደ ሀገራቸው በመመለስ ላይ የሚገኙ ሲሆን ከዚያ ቀደም ብለው በሰጡት ቃለ መጠይቅ የቻይናው ፕሬዝዳንት ኢራን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ እንዲኖራት ሊፈቀድላት አይገባም በሚለው ውሳኔ ተስማምተዋል ብለዋል፡፡

ትራምፕ አክለውም ኢራን የሆርሙዝ ሰርጥን መክፈት እንዳለባት ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ መናገራቸውን ጠቅሰው ሌሎች የሀገራቸው መሪዎች ሊፈቱት ያልቻሉትን በርካታ ችግሮች በሁለት ቀናት የቻይና ጉብኝት መፍታት መቻላቸውንም ጠቁመዋል፡፡

ምንም እንኳን ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ ከፕሬዝዳንት ትራምፕ ጋር ስለነበራቸው ንግግር ያሉት ነገር ባይኖርም የቻይና ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ቤጂንግ በኢራን ጦርነት መሰላቸቷን ገልጿል፡፡ ሮይተርስ እንደዘገበው፡፡

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
416

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram