avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
15.05.2026 13:13
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ በቤተ እስራኤላዊያን ላይ የሚፈፀም የዘረኝነት ጥቃትን እንደሚያወግዙ ተናገሩ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይሄን ያሉት ወደ እስራኤል ለመግባት ሲሉ ህይወታቸውን ያጡ ቤተ እስራኤላዊያንን ለማሰብ በተዘጋጀ አንድ የመታሰቢያ መርሃ ግብር ላይ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ በቤተ እስራኤላዊው ይማኑ ቢንያም ላይ የተፈፀመው ጥቃትን አውግዘው ገዳዮቹ በፍ/ቤት እንዲጠየቁ ጥሪ አቅርበዋል።

ቤኒያሚን ኔታናያሁ በቤተ እስራኤላዊያን ላይ የሚቃጣ ማናቸውንም ጥቃት እና መድልኦ እንደሚዋጉ በመድረኩ ላይ ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቤተ እስራኤላዊያንን ከመላው የእስራኤል ማህበረሰብ ጋር የማስተሳሰር ስር ውጤታማ መሆኑን ገልፀው ይሁን እንጂ አንዳንድ ያልተፈቱ ችግሮች እንዳሉ አንስተዋል። ዘገባው የኢየሩሳሌም ፖስት ነው።

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
479

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram