avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
15.05.2026 12:39
የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፊ ( ዶ/ር) በ2018 በጀት ዓመት 10 ወራት ውስጥ ከወጪ ንግድ 8.71 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን ተናገሩ።

ሚነስትሩ ባለፉት 10 ወራት 7.25 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ እንደነበረ አስታውሰው የዕቅዱን 120.17 በመቶ በማሳካት 8.71 ቢሊየን ዶላር ገቢ ተገኝቷል ብለዋል።

ሚነስትሩ አፈጻጸሙም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከተመዘገበው ጋር ሲነጻጸር የ43.32 በመቶ ብልጫ እንዳለው ተናገረዋል፡፡

ሚኒስትሩ ይህ ስኬት በዋናነት በንግድ ዘርፉ ላይ የወሰድናቸው የፖሊሲ እርምጃዎች ውጤት ነው ብለዋል።

መረጃው ከንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የተገኘ ነው።

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
429

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram