avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
14.05.2026 14:07
በመቅደላ ጦርነት ወቅት በብሪታኒያ የተወሰዱ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ በዛሬው ዕለት ተመልሰዋል፡፡

ከ158 ዓመታት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ የተመለሱት ቅርሶቹ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል፣ የልብስ ቁራጮች እንዲሁም የወርቅ አምባር መሆናቸው ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው በዚሁ ወቅት እንዳሉት ቅርሶቹ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲመለሱ የተደረገው የኢትዮጵያን የታሪክና የባህል አሻራዎች የማስመለስ ስራ አካል በመሆን ነው፡፡

ለረጅም ዘመናት በባዕድ ሀገር የቆዩት እነዚህ ቅርሶች ኢትዮጵያ የነበራትን ጥንታዊ ስልጣኔና ሉዓላዊነት የሚያሳዩ ትልልቅ የታሪክ ምስክሮች ናቸው የተባለ ሲሆን የቅርሶቹ መመለስ የኢትዮጵያን የታሪክ ባለቤትነትና የዲፕሎማሲ ስኬት የሚያሳይ ትልቅ ምዕራፍ ተደርጎ እንደሚወሰድም ተመላክቷል፡፡

የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው እና የኢትዮጵያ አርበኞች ማህበር አባላት ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በመገኘት ለቅርሶቹ ደማቅ አቀባበል ያደረጉ ሲሆን ታሪካዊ የሆኑና በተለያዩ ምክንያቶች ከሀገር ውጭ የወጡትን ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ የመመለስ ስራ በስፋት እንደሚሰራም ተጠቁሟል።

በነገው ዕለት ግንቦት 7/2018 ዓ.ም በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የቅርሶቹን ርክክብ እንደሚያደርግም ከባለስልጣኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
2
561

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram