avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
14.05.2026 13:20
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለሚወስዱ ተፈታኞች የመፈተኛ ክፍል መግቢያ ካርድ እንዲወስዱ ጥሪ አቀረበ።

የመፈተኛ ክፍል መግቢያ ካርድ በፈተና አስተዳደር ሲስተም ላይ (https://exam.eaes.et/) ከ03/09/2018 ዓ/ም ጀምሮ ለክልል ትምህርት ቢሮ፣ ለዞን ትምህርት መምሪያዎች እና ለትምህርት ቤት ተወካዮች መለቀቁን አገልግሎቱ ገልጿል።

አገልግሎቱ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በመጪው ሰኔ 24/2018 ዓ/ም ጀምሮ እንደሚሰጥ ገልጾ ተፈታኝ ተማሪዎች የመፈተኛ ክፍል መግቢያ ካርድ ከየትምህርት ቤታቸው እንዲወስዱ አሳስቧል።

ተፈታኞች በምዝገባ ወቅት በተፈታኙ ወይም በመዝጋቢው የተከሰተ የትምህርት መስክ፣ የጾታ፣ የፎቶ እና መሰል ማስተካከያዎች ካሉ ከግንቦት 30/2018 ዓ.ም በፊት እንዲያስተካክሉ አገልግሎቱ ጥሪ አቅርቧል።

ተፈታኞች በፈተና ወቅት ከአድሚሽን ካርድ በተጨማሪ የፋይዳ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል።

መረጃው ከትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የተገኘ ነው።

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
2
3 459

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram