avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
14.05.2026 13:12
በኢትዮጵያ ላይ ተጥሎ የነበረው የጦር መሳሪያ ማዕቀብ መነሳቱን የአሜሪካ መከላከያ ንግድ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት አስታወቀ።

ዳይሬክቶሬቱ ማዕቀብ መነሳቱን ይፋ ያደረገው የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ወደ ዋሽንግተን አቅንተው ከአሜሪካው አቻቸው ማርኮ ሩቢዮ ጋር በበርካታ ጉዳዮች ላይ መነጋገራቸውን ተከትሎ ነው።

በቅርቡ በሚወጣ የደንብ ለውጥ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የጦር መሳሪያ ዝውውር ውስጥ ከሚገኙ አገራት ተርታ ውስጥ እንድትሰረዝ የሚደረግ መሆኑ የተነገረ ሲሆን ይህ እገዳ በኢትዮጵያ ላይ ተጥሎ የነበረው በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ግጭት ጋር በተያያዘ መሆኑንም መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል፡፡

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
1
457

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram