avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
13.05.2026 14:44
🔸እስራኤል ትላንት በደቡብ ሊባኖስ በፈፀመችው ጥቃት በትንሹ 13 የአካባቢው ነዋሪዎች ተገደሉ።

🔸ከትላንቱ ጥቃት ከአንድ ቀን በፊት እስራኤል በናቤቴ ከተማ በፈፀመችው ጥቃት የተጐዱ ነዋሪዎችን ነፍስ ለማዳን የተሰማሩ እርዳታ ሰራተኞችም ተገድለዋል።

🔸የቤይሩት መንግስት በቅርቡ የተኩስ አቁም ከተደረገ በኋላ 380 ዜጐቿ በተጠናከረው የእስራኤል የአየር ድብደባ መገደላቸውን ይገልፃል።

🔸በአካባቢው የሚንቀሳቀሰው የሄዝቦላ መሪ ናይም ቃስም በፊናቸው ድርጅታቸው ጦርነቱ እስራኤልን ወደሚለበልብ የምድር ገሀነም እንቀይረዋለን እያሉ ነው።

🔸እስራኤል ዛሬ በፈፀመችው ጥቃትም ከቤይሩት ወደ ደቡባዊ ሊባኖስ በሚያመራ አውራ ጐዳና ላይ የነበረ ተሽከርካሪን በሚሳኤል መታለች።

🔸ኤፍፒ እንደሚለው እስራኤል ጥቃቱን እንዲህ ያፋፋመችው ከቤይሩት ጋር የደረሰችው ተኩስ አቁም ባለበት ሁኔታ ነው።

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
546

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram