🔸የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አዲስ አበባ ገቡ።
🔸የተመድ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ትናንት ምሽት አዲስ አበባ ቦሌ ዓለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
🔸ኢትዮጵያ እ.አ.አ ከ1945 ጀምሮ የተመድ መሥራች አባል ስትሆን፣ የጥቁር ሕዝቦች ኩራት እና የሉዓላዊነት ተምሳሌት በመሆን የሳን ፍራንሲስኮውን የድርጅቱን መመስረቻ ቻርተር ከፈረሙ 51 ሀገራት መካከል አንዷ ናት።
🔸ዋና ፀሐፊው በአዲስ አበባ በሚካሄደው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 80ኛ አመት የምስረታ በአል ላይ እንደሚታደሙ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
Обсуждение 0
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram