avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
12.05.2026 17:03
የኢትዮጵያ አየር መንገድ 6 ተጨማሪ ኤርባስ ኤ350 ሞዴል አውሮፕላኖችን ሊገዛ ነው።

ብሉምበርግ እንደሚለው አዲሶቹ የኤርባስ አውሮፕላኖች ሰፋ ያለ መጠን ወይም ዋይድ ቦዲ እንዲኖራቸው ሆነው የተፈበረኩ ናቸው።

አየር መንገዱ ከዚሁ የአውሮፓ አውሮፕላን አምራች ኩባንያ 20 በመጠናቸው አነስ ያሉትን ኤርባስ ኤ220 አውሮፕላኖችን ለመግዛት ማዘዙ ነው የተገለፀው።

እነዚህ አነስተኛ አውሮፕላኖች ለቅርብ በረራ አገልግሎት እንዲሰጡ የታለሙ መሆናቸው ተመልክቷል።

አየር መንገዱ ለግዥው በመጀመሪያ ደረጃ ድርድር ላይ ያለ ሲሆን ግዥው ሲጠናቀቅ አውሮፕላኖቹ አየር መንገዱ በአፍሪካም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያው ተመራጭ አውሮፕላን እንዲሆን ያስችለዋል ይላል ከቢዝነስ ዘገባው ብሉምበርግ ያገኘነው መረጃ።

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
491

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram