የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም የእኩለ ቀን የሀገር ውስጥ ዋና ዋና ዜናዎች ፦
🟢ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአፍሪካ ፎርዋርድ ጉባኤ ላይ ለመታደም ዛሬ ጠዋት ናይሮቢ ኬንያ ገብተዋል።
🟢የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ከኢትዮጵያው አቻቸው ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ጋር በዋሽንግተን ዲሲ ተገናኝተው መምከራቸውን ተናገሩ።
🟢በአሁኑ ወቅት ቻይና በኢትዮጵያ ያላት ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ከ 5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ሲደርስ ከ 2 ሺህ በላይ የቻይና ፕሮጀክቶች ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑ ተገልጿል።
🟢የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ኢትዮጵያና አሜሪካ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ቋሚ የሁለትዮሽ ምክክር ማዕቀፍ ስምምነት መፈራረማቸውን አስታወቀ።
🟢አንጋፋው ፖለቲከኛና የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር የነበሩት ዘገየ አስፋው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተገለጸ።
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
Обсуждение 0
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram