የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም የእኩለ ቀን የሀገር ውስጥ ዋና ዋና ዜናዎች
🟢ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ዋና ዳይሬክተር ክርስታሊና ጆርጂየቫ ጋር ተገናኝተው መወያየታቸውን ተናገሩ።
🟢የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በመጪው ረቡዕ በኢትዮጵያ ጉብኝት ሊያደርጉ መሆኑ ተነግሯል።
🟢የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል እና ከካናዳ ኤምባሲ ጋር በመተባበር ዜጎችን አሰልጥኖ ወደ ካናዳ ለመላክ ያደረገውን ስምምነት አስመልክቶ ዜጎች አጭበርባሪዎች ከሚያሰራጯቸው ሃሰተኛ መረጃዎች እራሳቸውን እንዲጠብቁ አሳስቧል፡፡
🟢በአማራ ክልል በሰዎች መነገድ እና በህገ-ወጥ መንገድ ዜጎችን ለስራ ወደ ውጭ ሀገር የመላክ ወንጀልን በዘላቂነት ለመከላከል የሚያስችል አዲስ የአሰራር ደንብ መጽደቁን የክልሉ ፍትህ ቢሮ አስታውቋል።
🟢በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 1 ሺ 612 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን የሰቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
Обсуждение 0
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram