የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ የሚያዚያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም የምሽት የሀገር ውስጥ ዋና ዋና ዜናዎች፦
🎯 የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ታደሰ ወረደ በብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ህጋዊ እውቅናው የተሰረዘው ህወሃት አመራሮች በህዝቡ ላይ ተጨማሪ ቀውስ የሚያመጣ እንቅስቃሴ ውስጥ መግባታቸውን ገለጹ፡፡
🎯 የሚያዝያ ወር 2018 ዓ.ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት መጠን 11 ነጥብ 7 በመቶ ሆኖ መመዝገቡን የኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት አስታውቋል።
🎯 የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በ2018 በጀት ዓመት ከተመደበለት መደበኛ በጀት 74 ነጥብ 8 በመቶ እንዲሁም የካፒታል በጀቱን 56 ነጥብ 8 በመቶውን መጠቀም መቻሉን ገልጿል።
🎯 ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በቀጣዩ የአውሮፓዊያን ዓመት የኢንቨስትመንት ወጪውን በመሸፈን ትርፍ ወደማግኘት ይሸጋገራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ኩባንያው ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል።
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
Обсуждение 0
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram