avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
08.05.2026 20:31
የሚያዝያ ወር 2018 ዓ.ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት መጠን 11 ነጥብ 7 በመቶ ሆኖ መመዝገቡን የኢትዮጵያ ስታስቲክስ አገልግሎት አስታውቋል።

በተለይም የምግብና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች ዋጋ 13 ነጥብ 5 በመቶ የጨመረ ሲሆን በዋናነት አትክልት፣ ስጋ፣ የወተት ተዋፅኦዎች፣ እንቁላል፣ ፍራፍሬ፣ ዘይትና ስኳር የመሳሰሉት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ በመጨመራቸው የተመዘገበ ጭማሪ መሆኑንንም ገልጿል።

ምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት 9 ነጥብ 1 በመቶ የደረሰ ሲሆን ትራንስፖርት 13 በመቶ፣ በኮሙዩኒኬሽን 9 ነጥብ 7 በመቶ፣ የምግብ ቤቶችና ሆቴሎች 10 ነጥብ 5 በመቶ እንዲሁም ሌሎች እቃዎችና አገልግሎቶች 15 ነጥብ 9 በመቶ ሆነው መመዝገባቸውን ከተቋሙ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

ይሀው የሚያዝያ ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ወር ጭማሬ ያሳየ ሲሆን የመጋቢት ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 9 ነጥብ 4 በመቶ ሆኖ መመዝገቡን አገልግሎቱ በወቅቱ አስታውቆ ነበር፡፡

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
3
745

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram