avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
08.05.2026 18:31
አሜሪካ በዓለምአቀፍ ደረጃ የነበራት ተቀባይነት ለሁለት ተከታታይ ዓመታት ማሽቆልቀሉ እንዲሁም ከሩሲያና እስራኤል ቀጥሎ የዓለም ስጋት ተደርጋ መቆጠር መጀመሯን አንድ ጥናት አመለከተ፡፡

አንድ የዴንማርክ የዴሞክራሲ ተቋም በ98 የዓለም ሀገራት የሚገኙ ከ94 ሺህ በላይ ሰዎችን በናሙናነት ወስጄ አከናወንኩት ባለው ዓለምአቀፍ ጥናት ፕሬዝዳንት ትራምፕ እየተከተሉት ያለው ፖሊሲ የአሜሪካን ዓለምአቀፍ ተቀባይነት እየሸረሸረው መሆኑን አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡

የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳደር በዓለም ሀገራት ላይ የጣለው ታሪፍ እንዲሁም ከአውሮፓ ሀገራትና ካናዳ ጋር የገባበት ውዝግብ ለአሜሪካ ተቀባይነትና ተሰሚነት ደረጃ መውረድ በጥናቱ እንደምክንያት የተቀመጡ ነጥቦች መሆናቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
548

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram