የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ የሚያዚያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም የእኩለ ቀን የሀገር ውስጥ ዋና ዋና ዜናዎች፦
🎯 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መገናኛ ብዙሃን በሰው ሰራሽ አስተውሎት እና በጥናት የታገዘ ጥልቅ ትንተና በማቅረብ፣ ከአርዕስት ሽያጭ ባለፈ ለሀገር አጀንዳዎች ትኩረት መስጠት አለባቸው ብለዋል።
🎯 በሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት የበጀት አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2019 በጀት ዓመት የበጀት ፍላጎትን ገምግሟል።
🎯 የኢትዮ-ጅቡቲ የንግድ ኮሪደር በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ቀጠናዊ የኢኮኖሚ ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የሁለቱን አገራት ታሪካዊ ወንድማማችነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሻግር ነው ተብሏል።
🎯 የኢትዮጵያን የገጠር ግብርና ትራንስፎርሜሽን ልማት ለመተግበር የግብርና ባንክ ማቋቋም የግድ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት አሳውቋል።
🎯 ባለፈው መጋቢት በተጠናቀቀው የሳፋሪኮም ኩባንያ በጀት ዓመት የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኪሳራ በግማሽ መቀነሱ ተነገረ።
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
Обсуждение 0
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram