avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
07.05.2026 18:17
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የአሽከርካሪዎች ብቃት መመዘኛ ሲስተም መተግበሪያ ወደስራ ሊገባ መሆኑን አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ ይሄን ያለው አዲሱ የአሽከርካሪዎች ብቃት መመዘኛ ሲስተም መተግበሪያ ላይ ያተኮረ ግምገማ ማድረጉን ባስታወቀበት መረጃው ላይ ነው፡፡

ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ተሳስሮ የተዘጋጀው ሲስተም አሽከርካሪዎች ባሉበት ቦታ ሆነው ምዝገባ የሚያካሂዱበት፣ የፈተና ቦታ እና ሰዓት እንዲያውቁ እንዲሁም ውጤታቸውን መልዕክት የሚያስችል ነው ተብሏል።

ሚኒስቴሩ ተመዝጋቢዎች ፈተና ከመውሰዳቸው በፊት የሲስተሙን አጠቃቀም በተመለከተ ስልጠና እንደሚሰጣቸውም ገልጿል።

የተዘጋጀው ይህ ሲስተም አሽከርካሪዎችን መዝግቦ፣ አሰልጥኖ እና ፈትኖ በመጨረሻም የብቃት ማረጋገጫ COC እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑንም ነው የገለጸው፡፡

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን የተዘጋጀው መተግበሪያ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተጠናቀቁ መሆኑን ገልፀው በቅርቡ በሲስተሙ አማካኝነት ምዝገባ እና ስልጠና እንደሚጀመርም ተናግረዋል።

መረጃው ከትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የተገኘ ነው፡፡

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
704

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram