avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
07.05.2026 14:24
የኢትየጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለፉት ዘጠኝ ወራት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ባከናወነው ስራ 9 ሺህ 588 ኪሎ ሜትር አዳዲስ የስርጭት መስመሮች ማስፋፊያ ወይም ዝርጋታ ማከናወኑን አስታውቋል፡፡

አገልግሎቱ ለጣቢያችን በላከው መግለጫ ከዚህ ውስጥ 3 ሺህ 518 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር፣ 6 ሺህ 69 ኪ.ሜ ደግሞ የዝቅተኛ መስመር ዝርጋታ የተከናወነ ሲሆን በተጨማሪም የኃይል አቅርቦቱን የሚያሳድጉ 3 ሺህ 683 የተለያዩ ዓቅም ያላቸው አዲስ የስርጭት ትራንስፎርመሮች ተከላ ተከናውኗል ብሏል፡፡

ነባሩ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት አቅም ከማሻሻልና የኃይል መቆራረጥን ከመቀነስ አኳያ 62 ሺህ 274 ኪ.ሜ የሚሸፍን የመካከለኛ መስመር እንዲሁም በ67 ሺህ 131 ትራንስፎርመሮች ላይ የቅድመ መከላከል ምርመራ መካሄዱንም ነው የገለጸው።

በዚህም ለኃይል መቆራረጥ መንስኤ ከሆኑ ግኝቶች ውስጥ በስርጭት ኔትወርክ ላይ ከተገኙት 92 ከመቶ፤ በትራንስፎርመሮች ደግሞ 86 ከመቶ የሚሆኑትን የማስተካከያ እርምጃዎች ተወስዶባቸዋል ብሏል።

የኢትየጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ መንስኤ የሆኑ ምክንያቶችን በጥናት ከመለየትና እርምጃ ከመውሰድ በተጨማሪ ያረጁ መስመሮችን መልሶ የመገንባት፣ ዓቅም የማሳደግና የማሻሻል እንዲሁም በዋናው ግሪድና በፀሃይ ኃይል አማራጭ አዳዲስ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማትን በከፍተኛ ወጪ እየገነባ መሆኑንን ገልጿል፡፡

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
1
628

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram