avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
07.05.2026 13:17
ፈረንሳይ የጦር ጄት ተሸካሚ መርከቦቿን ወደ ሆርሙዝ ሰርጥ ማንቀሳቀስ መጀመሯን አሳወቀች።

የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የሀገራቸው የባህር ኃይል ከብሪታንያ የባህር ኃይል ጋር በመቀናጀት በሆርሙዝ ሰርጥ ለመፈጸም ለታቀደው ወታደራዊ ተልዕኮ ዝግጁ ለመሆን የጦር መርከቡ አሁን ላይ ቀይ ባህር መድረሱን ነው ያሳወቁት፡፡

በኒውክለር ኃይል የምትንቀሳቀሰው ቻርልስ ዴጎል የፈረንሳይ የጦር ጄቶች ተሸካሚ ግዙፍ መርከብ እስከ አጃቢዎቿ ከቀይ ባህር ወደ ሆርሙዝ ሰርጥ ታቀናለች ተብሎ የሚጠበቅ ቢሆንም የፈረንሳይና ብሪታንያ ወታደራዊ ኦፕሬሽን ከአሜሪካ ይለያል ተብሏል፡፡

ሁለቱ ሀገራት በሆርሙዝ ሰርጥ የባህር ትራንስፖርት ደህንነትን ማረጋገጥን አላማ ያደረገ ወታደራዊ ኦፕሬሽን እንደሚፈጽሙ የገለጹት ማክሮን ጉዳዩን በተመለከተም ከኢራኑ ፕሬዝዳንት መሱድ ፔዜሽኪያን ጋር መነጋገራቸውን ጠቁመዋል፡፡

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
2
608

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram