የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የባንኩ ደንበኞች ከባንክ ነው በሚል ከሚደውሉ አጭበርባሪዎች እንዲጠነቀቁ አሳስቧል።
የባንኩ ደንበኞች ከባንክ ነው በሚል የሚደርሳቸውን የስልክ ጥሪ ትክክለኛነት ወደ ባንኩ ቅርንጫፍ በመሄድ ወይም ወደ 951 በመደወል ሳያረጋግጡ ምንም ዓይነት እርምጃ እንዳይወስዱ ባንኩ አስጠንቅቋል።
ባንኩ ደንበኞቹ የባንክ መረጃቸውን በስልክ ለማንም እንዳይሰጡ እና የባንኩን መተግበሪያዎች ከ ፕሌይ ስቶር እና አፕ ስቶር ብቻ አውርደው እንዲጠቀሙ መክሯል።
የባንኩ ደንበኞች ከማህበራዊ ሚዲያ ጓደኛ የሚመጣን የእርዳታ ጥሪ በጥንቃቄ እንዲፈትሹ ባንኩ አሳስቧል።
መረጃው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተገኘ ነው።
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
Обсуждение 0
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram