avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
07.05.2026 13:10
ኢራን የአሜሪካን አዲሱን የሰላም ዕቅድ እያጤነችበት መሆኑን አሳውቃለች።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፊናቸው የኢራን ጦርነት በአስቸኳይ እንደሚቆም ያላቸውን ተስፋ ጠቁመው በርካታ ሰዎችም የኢራንን የኒውክለር ጦር መሣሪያ ባለቤትነት ህልም ማክሸፍን የተመለከተውን ዓላማቸውን እንደሚደግፉ ገልጸዋል፡፡

የቢቢሲ ዘገባ እንደሚያመለክተው አሜሪካ ያቀረበችውን ባለ 14 ነጥቦች የመግባቢያ ስምምነት ኢራን ትቀበላለች የሚል ተስፋ ያጫረች ሲሆን ይህም ስምምነት በሀገሪቱ የኒውክለር ፕሮግራም ዙሪያ በዝርዝር መነጋገር የሚቻልበትን ማዕቀፍ ያበጃል ተብሏል፡፡

የኢራን ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ የመግባቢያ ስምምነቱን በተመለከተ የቴህራንን አቋም ለአሸማጋይዋ ፓኪስታን እንደሚያስረክቡ ሲገልጹ አንድ ኢራን ፓርላማ አባል ደግሞ መግባቢያ ስምምነቱን ፍፁም ቅዠት ሲሉ አጣጥለውታል፡፡

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
532

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram