avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
06.05.2026 13:00
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ትናንት ባወጣው መግለጫ ሱዳን በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ እንዲሁም በጦሩ ቃል አቀባይ በኩል በኢትዮጵያ ላይ ያቀረበችው ክስ መሰረተ ቢስ ክስ ነው ሲል አሳውቋል፡፡

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አክሎም የኢትዮጵያ መንግስት የሁለቱን ሀገራት ህዝቦች የረጅም ጊዜ ወንድማማችነትና ታሪካዊ ትስስር በማክበር፤ በሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት ተሳታፊ በሆኑ ኃይሎች በኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና ብሄራዊ ደህንነት ላይ የተፈጸሙ ጥሰቶችን ይፋ ሳያደርግ በትዕግስት ማለፉን አስታውቋል።

ከጥሰቶች ውስጥ የህወሓት ቅጥረኞችን በሱዳን ጦርነት ውስጥ በስፋት ማሳተፍ አንዱ መሆኑንና ሀገሪቱ የተለያዩ ጸረ ኢትዮጵያ ኃይሎች መናኸሪያ እየሆነች መምጣቷን የሚያሳዩ ተአማኒነት ያላቸው ማስረጃዎች መኖራቸውንም ጠቁሟል።

የሱዳን ጦር ለእነዚህ የህወሓት ቅጥረኞች የጦር መሳሪያና የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ በኢትዮጵያ ምዕራባዊ ድንበር በኩል ጥቃት እንዲፈጽሙ ሁኔታዎችን ማመቻቸቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።

የሱዳን ጦር ባለስልጣናት በኢትዮጵያ ላይ የሚያቀርቧቸው ክሶች የራሳቸውን አላማ ለማራመድ በሚንቀሳቀሱ የውጭ ኃይሎች ግፊትና ትዕዛዝ የሚፈጸሙ መሆናቸውንም የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው አብራርቷል።

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
524

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram