avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
05.05.2026 17:48
የገንዘብ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ ክምችት 3.4 ቢሊየን ዶላር መድረሱን አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ ይሄን ያስታወቀው ዛሬ ባወጣው የ18 ወራት ጥቅል ሪፖርቱ ላይ ነው።

ሚኒስቴሩ ከፈረንጆቹ 2024 እስከ 2025 አመት ባሉት ጊዜያት ውስጥ የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ ክምችት በ240 በመቶ ማደጉን ገልጿል።

ሚኒስቴሩ የወጪ ንግድ ገቢ ማደጉ ፣ የሃዋላ ገቢ መጨመሩ ፣ የውጭ እርዳታ እና ብድር እያደገ በመምጣቱ የሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ጨምሯል ብሏል።

ሚኒስቴሩ በመደበኛው እና በትይዩ ገበያው መካከል ያለው የውጭ ምንዛሬ ልዩነት መጥበቡን ገልጿል።

ሚኒስቴሩ ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ 2024/25 በጀት ዓመት ከ6 ቢሊየን ዶላር በላይ ከሃዋላ አግኝታለች ብሏል።

መረጃው ከገንዘብ ሚኒስቴር የተገኘ ነው፡፡

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
😁 1
594

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram