avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
05.05.2026 14:16
የማሊ መከላከያ ሚኒስትር መገደላቸውን ተከትሎ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት አሳሚ ጎይታ እራሳቸውን የሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስትር አድርገው መሾማቸው ተነገረ።

የሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስትር ሳዶ ካማራ ታጣቂዎች በመላ ሀገሪቱ ላይ በከፈቱት የተቀናጀ ጥቃት ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገደላቸው የተሰማው ባለፈው ሳምንት ነበር፡፡

ይህንንም ተከትሎ በመፈንቅለ መንግስት ላለፉት 4 ዓመታት የሀገሪቱ መሪ የሆኑት አሳሚ ጎይታ እራሳቸውን የሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስትር አድርገው የሰየሙ ሲሆን የሀገሪቱ ጦር አዛዥ ጄኔራል ኦማር ዲያራ ረዳታቸው ይሆናሉ ተብሏል፡፡

ፕሬዝዳንቱ ሁለቱን የሀገሪቱ ስልጣን ለመቆጣጠር የተገደዱት መንበራቸው በመነቅነቁ ስልጣናቸውን ለማጠናከርና ስር ለማስያዝ መሆኑን ጠቅሶ የዘገበው ቢቢሲ ነው፡፡

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
572

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram