በደቡብ አፍሪካ የተቀሰቀሰውን ፀረ ስደተኞች ተቃውሞ ተከትሎ በስደተኞች ላይ በሚፈፀም ግድያና ዝርፊያ ምክንያት ናይጄሪያ ከደቡብ አፍሪካ መውጣት የሚፈልጉ ዜጎቿን ለማውጣት መሰናዳቷን አሳወቀች፡፡
ናይጄሪያ የደቡብ አፍሪካ ባለስልጣናት ስለጉዳዩ ዝርዝር መረጃዎችን በአስቸኳይ እንዲሰጧት መጠየቋን የገለጸች ሲሆን ነገር ግን ዜጎቿን ለመታደግ ፈቃደኛ የሆኑ ናይጄሪያዊያንን ከደቡብ አፍሪካ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ማቀዷን ይፋ አድርጋለች፡፡
ባለፈው ሳምንት በትንሹ 2 ናይጄሪያዊያንና 4 ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በደቡብ አፍሪካ መገደላቸውን ያስታወሰው ቢቢሲ በሀገሪቱ በዚህ ሳምንትም የተጠሩ ፀረ ስደተኞች ተቃውሞዎች ተጨማሪ የስደተኞችን ሕይወት እንዳይቀጥፉ መሰጋቱን ጠቁሟል፡፡
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
Обсуждение 0
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram