የገቢዎች ሚኒስቴር ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታወቀ።
የጉምሩክ ኮሚሽን ከሚያዚያ 11 እስከ ሚያዚያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረገው ክትትል በጅግጅጋ ፣ በአዲስ አበባ ኤርፖርት እና በኮምቦልቻ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች 386.2 ሚሊዮን ብር የገቢ የኮንትሮባንድ እቃዎች እና 14.5 ሚሊዮን ብር የወጭ፤ በድምሩ 400.7 ሚሊዮን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ተይዘዋል፡፡
በቁጥጥር ስር ከዋሉት የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መካከል አዳዲስ እና ልባሽ ጨርቆች፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ የግብርና ምርቶች፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ፣ የመዋቢያ እቃዎች፣ አደንዛዥ እጾች፣ መድኃኒት፣ የተለያዩ ማዕድናት፣ ነዳጅ፣ የቁም እንስሳት እና የውጭ ሀገር ገንዘቦች ይገኙበታል ተብሏል፡፡
የኮንትሮባንድ እቃዎቹን ሲያዘዋውሩ የተገኙ 26 ተጠርጣሪዎች እና 10 ተሽከርካሪዎችም በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
መረጃው ከገቢዎች ሚኒስቴር የተገኘ ነው።
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
Обсуждение 0
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram