ሳኡዲ አረቢያ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ወደ ሀገሯ በሕገወጥ መንገድ ሊገቡ የነበሩ 1330 ዜጐችን በቁጥጥር ስር ማዋሏ ተነገረ።
ሪያድ ባለፈው ሳምንት በቁጥጥር ስር ካዋለቻቸው 1330 ስደተኞች ውስጥ 54 በመቶ ኢትዮጵያውያን ፣43 በመቶ የየመን ዜጐች እና ቀሪዎቹ የሌሎች ሀገራት ዜጐች ናቸው ተብሏል።
ሳኡዲ አረቢያ ባለፈው ሳምንት ብቻ የሀገሪቱን ህግ ጥሰዋል ያለቻቸውን 11,300 በቁጥጥር ስር ማዋሏን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
የሳኡዲ አረቢያ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ማንኛውም የሀገሪቱ ዜጋ በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሳኡዲ አረቢያ እንዲገቡ ካደረገ እስከ 267 ሺ ዶላር መቀጮ እንደሚጥል በዘገባው ተገልጿል።
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
Обсуждение 0
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram