avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
04.05.2026 12:44
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፔክስ የመንገደኞች ምርጫ አዋርድ 2026 ‘የአፍሪካ ምርጥ አየር መንገድ’ በመባል ተሸላሚ መሆኑን አስታወቀ።


ይህ ሽልማት አየር መንገዱ የተሳለጠ፣ ምቹ እና አስተማማኝ አገልግሎት ለደንበኞቹ ለማቅረብ ያለውን ያልተቋረጠ ትጋት ከማሳየቱ ባሻገር በአቪዬሽን አገልግሎት ዘርፉ ያለውን መሪነት ይበልጥ የሚያጠናክር ነው ተብሏል።

የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው አየር መንገዱ የአፍሪካ ምርጥ አየር መንገድ ተብሎ መሸለሙ አስደሳች መሆኑን ገልፀው ሽልማቱ ይበልጥ እንዲተጋ በእጅጉ ያበረታተዋል ብለዋል።

መረጃው ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የተገኘ ነው።

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
2
794

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram