avatar
EBSTV NEWS
@ebstvnews
03.05.2026 17:10
ባለፉት 9 ወራት በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውርና በማጭበርበር ወንጀል ሊመዘበር የነበረ 48 ቢሊየን ብር ከምዝበራ ማዳን መቻሉን የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት አስታውቋል፡፡

ከ400 በላይ የወንጀሉ ተጠርጣሪዎች የሚያንቀሳቅሷቸው 2 ሺህ 340 የባንክ ሂሳቦች መታገዳቸውን አገልግሎቱ ገልጿል፡፡

እንዲሁም በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ ማጭበርበር እና ተያያዥ የፋይናንስ ወንጀሎች የተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ ምርመራ እየተከናወነ መሆኑን የተቋሙ መረጃ ያመለክታል።

አገልግሎት መስሪያ ቤቱ ደኅንነቱ የተጠበቀ የፋይናንስ ስርዓት እንዲኖር በዘመናዊ ስርዓት የሚያደርገውን ክትትል አጠናክሮ እንደሚቀጥል እና በፋይናንስ ዘርፉ ላይ የሚከሰቱ ህገወጥ እንቅስቃሴዎችን በመከታተል ፈጣን ምላሽ ለመስጠት እየሰራ እንደሚገኝም ጠቁሟል።

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
3 881

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

EBSTV NEWS

5.5K
Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.

https://t.me/ebstvworldwide

Inbox - @EbswhatsnewBot
Открыть в Telegram