ኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ የሚያዚያ 23 ቀን 2018 ዓ.ም የምሽት የሀገር ውስጥ ዋና ዋና ዜናዎች
✅የአውሮፓ ኅብረት በትግራይ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በቅርብ እየተከታተልኩ ነው አለ።
✅በኢትዮጵያ የሰነደ መዋእለ ንዋይ ገበያ ውስጥ ለመካተት በምዝገባ ላይ ካሉ ኩባንያዎች ውስጥ መስፈርቱን አሟልተው አክሲዮኖቻቸውን ለማገበያየት ፈቃድ የተሰጣቸው 6ቱ ብቻ ስለመሆናቸው ተነግሯል፡፡
✅የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ከኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘ የተቀናጀ የሚድያ ቁጥጥርና አስተዳደር ስርዓት ቴክኖሎጂ በይፋ ስራ አስጀምሯል።
✅በኢትዮጵያ ከአንድ ሺህ ህፃናት ውስጥ 73ቱ ህፃናት በፎሊክ አሲድ እጥረት ምክንያት በሚከሰት የነርቭ ዘንግ ችግር እንደሚጠቁ ተገልጿል፡፡
✅በሚቀጥሉት አሥር ቀናት በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ለዝናብ መፈጠር አስተዋጽኦ የሚያደርጉ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
Обсуждение 0
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram