በኢራን ጦርነት ምክንያት የአፈር ማዳበሪያና እሱን ለማምረት የሚያስፈልጉ ጥሬ ዕቃዎች ፍሰት በመስተጓጎሉ ዓለማችን ለከፍተኛ የምግብ እጥረት ልትጋለጥ ትችላለች ተብሏል።
ትልቁ የአፈረ ማዳበሪያ አምራች ያራ ኩባንያ ባለቤት ቬይን ቶሬ እንደገለጹት ከጦርነቱ ባሻገር አሁን ላይ የሆርሙዝ ሰርጥ ተዘግቶ መቀጠሉ በዓለማችን የምግብ ምርት ላይ የሚኖረው ጉዳት የከፋ ሊሆን ይችላል፡፡
እንደ ያራው ባለቤት ከሆነ በአፈር ማዳበሪያ ምርትና ፍሰት መስተጓጎል ምክንያት በዓለምአቀፍ ደረጃ በየሳምንቱ 10 ቢሊዮን ጊዜ የሚቀርብ ምግብ የሚጠፋ ሲሆን የችግሩ ቀዳሚ ተጠቂዎች ደግሞ ደሀ ሀገራት ናቸው፡፡
ያለበቂ የአፈር ማዳበሪያ የሚመረቱ ምርቶች ምርታማነታቸው የሚቀንስ መሆኑን ተከትሎ በቀጣይ የረሃብ ጦርነት እንዳይቀሰቀስ የዓለም ሀገራት በጋራ እርምጃ መውሰድ እንደሚጠበቅባቸው ጠቅሶ የዘገበው ቢቢሲ ነው፡፡
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
Обсуждение 0
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram