የጋምቤላ ክልል ማዕድን ቢሮ 5 ሺህ 535 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ማስገባቱን አስታወቀ።
ቢሮው ይሄን ያለው የ2018 በጀት ዓመት 9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ነው።
በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በዘርፉ የታየው አፈፃፀም ከቀዳሚው ዓመት ጋር ሲነፃጸር ከአንድ ሺህ 278 ኪሎ ግራም በላይ የወርቅ ምርት ብልጫ ያለው መሆኑ ተገልጿል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ የወርቅ ማዕድን ሀብት እንደ ሀገር ልዩ ትኩረት ከተሰጣቸው ዘርፎች አንዱ ነው መሆኑን ጠቅሰው በክልሉ ያለውን የወርቅ ማዕድን ሀብት ልማት በማዘመን ጥቅም ላይ ለማዋል ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ርዕሰ መስተዳድሯ በቀጣይ ሶስት ወራትም 1 ሺህ 500 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
@ebstvnews
www.ebstv.tv
Обсуждение 0
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram