avatar
Commercial Bank of Ethiopia - Official
@combankethofficial
08.04.2026 10:01
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክና የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳር ፋይናንስ ቢሮ በኢንተርኔት ባንኪንግ አገልግሎት አብረው ለመስራት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ፡፡
• ስምምነቱ የቢሮውን የፋይናንስ ቁጥጥርና አሰራር ዘመናዊ ለማድረግ ይረዳል ተብሏል፡፡
*****************


በስምምነቱ ወቅት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሆል ሴል ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር እስክንድር አስፋው በሰጡት መግለጫ ባንካችን የዲጅታል ኢትዮጵያ ግብን እውን ለማድረግ ከተለያዩ ተቋማት ጋር እየሰራ እንደሚገኝና ይህ ስምምነት የዚሁ አካል መሆኑን ገልፀዋል፡፡

99 በመቶ የሚሆኑት የፌደራል ተቋማት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የኢንተርኔት ባንኪንግ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረው፣ የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር የፋይናንስ ቢሮም የዚሁ አገልግሎት ተጠቃሚ በመሆኑ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ዘመናዊና ቀልጣፋ እንደሚያደርግ ገልጸዋል፡፡

መስተዳደሩ በ119 ወረዳዎች፤ 600 ትምህርት ቤቶችና ጤና ጣቢያዎች ስም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያለውን ሂሳብ በተማከለ መልኩ በኢንተርኔት ባንኪንግ አገልግሎት ለማንቀሳቀስ ስምምነቱ እንደሚያስችል ዶ/ር እስክንድር አመልክተዋል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፋይናነስ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን በበኩላቸው እንደተናገሩት በከተማው የሚካሄዱ በርካታ የልማት ስራዎችን የፋይናንስ እንቅስቃሴን 24 ሰዓት ለመቆጣጥርና ለማስተዳዳር የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኢንተርኔት ባንኪንግ አገልግሎት ትልቅ ሚና አለው፡፡

ስምምነቱ ግልጸኝነትን፤ ተጠያቂነትንና ቀልጣፋ አሰራርን ስለሚያሰፍን የመስተዳድሩን የፋይናንስ ግቦች ለማሳካት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ተመራጭ ማድረጋችን ትክክለጫ አካሄድ ነው ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በውሃና የኤሌክትሪክ ፍጆታ ክፍያ፣ በትራፊክ ቅጣት ክፍያዎች፣ በቤት ልማት እና በሌሎች ዘርፎችም ከመስተዳድሩ ጋር በዲጅታል ባንኪንግ በኩል አብሮ እየሰራ ነውም ተብሏል፡፡

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ በዲጅታል ባንኪንግ አማራጮች በከ15.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ገንዘብ መዘዋወሩ ታውቋል፡፡
17
👍 5
👏 1
1 6 17.5K
avatar
Commercial Bank of Ethiopia - Official
@combankethofficial
08.04.2026 08:39
የበዓል ሸመታዎን በሲቢኢ ቪዛ ካርድ እየፈፀሙ
ወደ ዓለም ዋንጫ ለመሄድ ይዘጋጁ!
***

በአገልግሎት መስጫ ማዕከላት እና የግብይት ስፍራዎች ለሚያከናውኑት ግዢ በሲቢኢ ፖስ እና ሌሎች የክፍያ አማራጮች ከ1 ሺ ብር ጀምሮ በሲቢኢ ቪዛ ካርድዎ (የኤቲኤም ካርድዎ) ክፍያ ሲፈፅሙ ሙሉ ወጪዎ ተሸፍኖ የፊፋ 2026™ የዓለም ዋንጫ ጉዞን ለማሸነፍ ዕጣ ውስጥ ይካተታሉ።

ደጋግመው ክፍያ ሲፈፅሙ እድልዎን ያሰፋሉ!

የሽልማት ዕድሉ ከመጋቢት 5 እስከ ሚያዝያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ብቻ ይቆያል!

ደንብ እና ሁኔታዎች ተፈፃሚ ናቸው!

መልካም እድል!
***

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
#በሲቢኢቪዛካርድዎይክፈሉ #የ2026የፊፋዓለምዋንጫ

Make your holiday shopping with your CBE Visa Card and get ready to go to the World Cup!
*********
Make purchases of 1,000 Birr or more at POS or other payment channels using your CBE Visa Card and enter the draw to win a fully sponsored trip to the FIFA World Cup 2026™—for you and one person of your choice.

The more you pay, the higher your chances!

Promo runs from March 14 to April 14, 2026. T&Cs apply.

Good Luck!
****

Commercial Bank of Ethiopia
The Bank You Can Always Rely On!

#cbe #cardbanking #banking #ethiopia #visa
#PayWithCBEVisaCard #FIFAWorldCup2026
26
👍 1
👏 1
2 17.6K
avatar
Commercial Bank of Ethiopia - Official
@combankethofficial
08.04.2026 06:37
የፋሲካ በዓል ስጦታችን እንዳያመልጥዎ..............
********

ለበዓል
ከውጭ ሀገራት በ #EthioDirect ፣ #CashGo ፣ #FastPay ፣ #WegenSend ፣ #botim እና #LakiRemit የገንዘብ መላኪያ መተግበሪያዎች እንዲሁም ከባንካችን ጋር በሚሠሩ ዓለም አቀፍ የሐዋላ አስተላላፊዎች በኩል ገንዘብ ሲላክልዎ

🎁 በእያንዳንዱ ዶላር 10 ብር ጉርሻ
🎁 ከ50 ዶላር በላይ ሲላክልዎ በየቀኑ የ10,000 ብር ሽልማት
🎁 ከ500 ዶላር በላይ ሲላክልዎ ደግሞ በየሳምንቱ 50,000 ብር ሽልማት በዕጣ ያገኛሉ!

በእጅዎ ያለውን የውጭ ሀገር ገንዘብ በባንካችን ቅርንጫፎች ሲመነዝሩም ተጨማሪ ጉርሻ ይበረከትልዎታል!

የሽልማት ዕድሉ ከመጋቢት 26 እስከ ሚያዚያ 24፣ 2018 ዓ.ም ብቻ ይቆያል!

ከወዲሁ መልካም የትንሣኤ በዓል እንመኝልዎታለን!
*********
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
#cbe #easter
24
👍 3
8 4 18.4K
avatar
Commercial Bank of Ethiopia - Official
@combankethofficial
08.04.2026 04:55
10 ብር ተጨማሪ ጉርሻ!
(ዛሬ አንድ የአሜሪካ ዶላር 166.1262 ብር)
****

ውድ ደንበኞቻችን፡

ከውጭ ሀገራት በ #EthioDirect ፣ #CashGo ፣ #FastPay ፣ #WegenSend ፣ #botim እና #LakiRemit የገንዘብ መላኪያ መተግበሪያዎች እንዲሁም ከባንካችን ጋር በሚሠሩ ዓለም አቀፍ የሐዋላ አስተላላፊዎች በኩል ገንዘብ ሲላክልዎ በእለታዊ የውጭ ምንዛሬ የመሸጫ ተመን ላይ 10 ብር ተጨማሪ ጉርሻ የምናበረክትልዎት መሆኑን በደስታ እንገልፃለን!

ዛሬ ሲልኩ በባንካችን አንድ የአሜሪካ ዶላር ከጉርሻ ጋር በ166.1262 ብር ይመነዘራል!
***
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!

For more currency exchange rates:

https://combanketh.et/exchange-rates?srcPage=home

#exchangerate #CBE #commercialbankofethiopia #Birr #rate #currency #Ethiopia
29
👍 2
😁 1
1 10 19.9K
avatar
Commercial Bank of Ethiopia - Official
@combankethofficial
07.04.2026 22:17
የጥንቃቄ መልዕክት ከባንካችሁ!
ክቡራን ደንበኞቻችን ፤
********************
በአሁኑ የዲጂታል ዘመን ስልክዎ የባንክ ሂሳብዎ መሆኑን ያውቃሉ? በጥቃቅን ስህተቶች ለዘመናት የቆጠቡትን ጥሪት ለነጣቂዎች አሳልፈው እንዳይሰጡ የሚከተሉትን ጥንቃቄዎች ያድርጉ፦
1) ሚስጥራዊነትን ይጠብቁ፦ የባንክ ሂሳብ ቁጥርዎን፣ የሞባይል ባንኪንግ የይለፍ ቃል (Password/PIN) እና በስልክዎ የሚላኩ የማረጋገጫ ቁጥሮችን (OTP) ለማንም አሳልፈው አይስጡ።
2) ከአጠራጣሪ ጥሪዎችና ሊንኮች ይጠንቀቁ፦ ባንኩ በስልክ ደውሎ ሚስጥራዊ ቁጥርዎን አይጠይቅም። ማንኛውንም አጠራጣሪ ሊንክ አይክፈቱ፤ የማያውቁትን ስልክ አይመልሱ።
3) ስልክዎ ሲጠፋ፦ ስልክዎ ቢጠፋ ወይም ቢሰረቅ በአፋጣኝ በ951 በመደወል ወይም በአቅራቢያዎ በሚገኝ ቅርንጫፍ በመቅረብ የባንክ አገልግሎትዎ እንዲታገድ ያድርጉ።
4) ጠንካራ የይለፍ ቃል ይጠቀሙ፦ የሞባይል ባንኪንግ የይለፍ ቃልዎን በቀላሉ የማይገመት (ቢያንስ 6 ዲጂት) ያድርጉ። ከባንክ የተላከልዎትን ጊዜያዊ ቁጥር ወዲያውኑ ይቀይሩ፤ ከስልክዎም ላይ ያጥፉት።
5) ስልክዎን ለሰው አይስጡ፦ ስልክዎን ለጥገና ወይም ለሌላ ጉዳይ ለሰው ሰጥተው ሲቀበሉ አጠራጣሪ መተግበሪያዎች (Apps) አለመጫናቸውን ያረጋግጡ።
6) የማህበራዊ ሚዲያ ደህንነት፦ በስራ ማስታወቂያ ወይም በሽልማት ስም የሚላኩ የባንክ ወይም የቴሌግራም/ዋትስአፕ ማረጋገጫ ቁጥሮችን ለሌላ አካል በመስጠት የባንክ ሒሳብዎ ተጠልፎ ለወንጀል እንዳይውል ይጠንቀቁ።
ሁልጊዜም ንቁ እና ጠንቃቃ በመሆን ገንዘብዎን ይጠብቁ!
#የኢትዮጵያ_ንግድ_ባንክ #cbe #FraudAlert
35
👍 10
11 7 4.8K
avatar
Commercial Bank of Ethiopia - Official
@combankethofficial
07.04.2026 21:57
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ዜጎች በሀገሪቱ የልማት ስራዎች ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ ምቹ ሁኔታዎችን እየፈጠረ እንደሚገኝ ተገለጸ።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኦሮሚያ ዲያስፖራ ማህበር ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ።
**************************
በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቢዝነስ ኤክስኪዩቲቭ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ደረጄ ፉፋ እንደገለጹት፤ ስምምነቱ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሀገራዊ ልማት ላይ ያላቸውን ሚና ለማጎልበት ትልቅ ፋይዳ አለው።

ስምምነቱ ዲያስፖራው በሀገር ውስጥ ኢንቨስትመንት ላይ በስፋት እንዲሰማራ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ያለመ እንደሆነ ያብራሩት አቶ ደረጄ ባንካችን ለዲያስፖራው ማህበረሰብ የሚመጥኑ የቁጠባ፣ የብድርና የገንዘብ መላኪያ አማራጮችን በስፋት ማመቻቸቱንም አክለዋል።

የባንካችን የሪቴይል ባንኪንግ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ደሳለኝ አለሙ በበኩላቸው፤ ማህበሩ ባንካችን የሚያቀርባቸውን አገልግሎቶች ለዲያስፖራው ተደራሽ ለማድረግ እንደ ድልድይ ሆኖ እንደሚያገለግል ገልጸዋል።
ዲያስፖራው የመኪናና የቤት ግዢ ብቻ ሳይሆን፣ ከአነስተኛ እስከ ትላልቅ ፕሮጀክቶች ላይ እንዲሰማራ የሚያስችሉ ቅድመ ሁኔታዎች መመቻቸታቸውንም አስረድተዋል።

የኦሮሚያ ዲያስፖራ ማህበር ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ሳራ ሀሰን በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለዲያስፖራው ልዩ ቅርንጫፎችን ከመክፈት ጀምሮ እንደ ኢትዮ ዳይሬክት (EthioDirect) እና ሲቢኢ ኮኔክት (CBEConect) ያሉ ዘመናዊ የገንዘብ መላኪያ መተግበሪያዎችን ማቅረቡ በትብብር ለመስራት እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል።

ባንኩ የሀገር አለኝታ መሆኑን የጠቀሱት ፕሬዝዳንቷ፤ ዲያስፖራው የአገልግሎቶቹ ተጠቃሚ በመሆን በሀገሩ ልማት ላይ አሻራውን እንዲያኖር ጥሪ አቅርበዋል።
#የኢትዮጵያ_ንግድ_ባንክ #cbe #diaspora #oromia_diaspora
11
👏 2
4.5K
avatar
Commercial Bank of Ethiopia - Official
@combankethofficial
07.04.2026 17:53
ሁሉንም ባሉበት
በሲቢኢ ዲጂታል የባንክ አገልግሎት
ገንዘብዎን እና ጊዜዎን ይቆጥቡ!
************

�� ገንዘብ ለመላክ እና የተለያዩ ክፍያዎችን ለመፈፀም
�� የተለያዩ የባንክ አገልግሎቶችን ለማግኘት
�� ግብር እና ለተለያዩ መንግስታዊ አገልግሎቶች ክፍያ ለመፈፀም
�� የመብራት እና ውሀ ክፍያ ለመፈፀም
�� የጉዞ ትኬት ክፍያ ለመፈፀም
�� የአየር ሰዓት ለመሙላት
�� .....................

የትም መሄድ ሳይጠበቅብዎት ካሉበት ሆነው ከጥሬ ገንዘብ ነፃ
በሲቢኢ ዲጂታል የባንክ አገልግሎት አማራጮች ይጠቀሙ!
**********
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
#cbe #digitalbanking #cashless
21
👍 4
13 1 8.7K

Commercial Bank of Ethiopia - Official

198.1K
Commercial Bank of Ethiopia is the leading bank in Ethiopia, established in 1942. Pioneer to introduce modern banking to the country with 1,971 branches and service outlet across the country.
@ www.facebook*.com/combanketh
@ www.twitter.com/combankethiopia
* Принадлежит организации Meta, которая признана экстремистской и запрещена на территории РФ
Открыть в Telegram