avatar
Ethiopian News Agency
@EthiopianNewsA
12.04.2026 11:56
የትንሳኤ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 4/2018 (ኢዜአ)፡- የትንሳኤ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል።

በዓሉ ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ የተነሳበት ዕለት የሚታወስበት ነው።

የትንሳኤ በዓልን አስመልክቶ የኃይማኖት አባቶች ባስተላለፉት መልዕክት ሕዝበ ክርስቲያኑ የትንሳኤን በዓል የአንድነትና የቸርነት እሴቶችን በማጎልበት፣ በመረዳዳትና በአብሮነት እንዲያሳልፍ አባታዊ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

ሕዝበ ክርስቲያኑ ከቂም በቀልና ከጥላቻ በመራቅ፣ ከሌሎች ወንድምና እህቶቻቸው ጋር በመተባበር ለሀገር ሰላምና ፍቅር መስራት እንዳለበት አመልክተዋል።

የሃይማኖት አባቶቹ በመልዕክታቸው ማጠቃለያ ላይ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የደስታ እንዲሆን ለሁሉም የክርስትና እምነት ተከታዮች መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

የትንሳኤ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በተለያዩ ዝግጅቶች በመላው ኢትዮጵያ እየተከበረ ይገኛል።
1 1.2K

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

Ethiopian News Agency

21.3K
Ethiopian News Agency official telegram channel
Открыть в Telegram