Ethiopian News Agency @EthiopianNewsA 09.04.2026 15:00 Скопировать Пожаловаться ኢትዮ ቴሌኮም "ቶሎ" የተሰኘ የፈጣን መንገድ የክፍያ ሥርዓት በቴሌብር አስጀመረ አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 1/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮ ቴሌኮም "ቶሎ" የተሰኘ የፈጣን መንገድ የክፍያ ሥርዓትን በቴሌ ብር አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን ዲጂታል የክፍያ ስርአት ስራ አስጀመረ። ኢትዮ ቴሌኮም "ቶሎ" የተሰኘው የክፍያ ስርአት የማስጀመር መርሀ ግብር አካሂዷል። ኢትዮ-ቴሌኮም ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚያስችሉ የተለያዩ አገልግሎቶችን እያስተዋወቀ መሆኑን በወቅቱ ተገልጿል። ኢትዮ-ቴሌኮም ከመደበኛ የቴሌኮም አገልግሎት ባሻገር ቀልጣፋ፣ምቹና ወጪ ቆጣቢ አገልግሎት በማቅረብ የፋይናንስ ዘርፉን እየደገፈ መሆኑንም የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ አስረድተዋል። በዚህም የሀገረን ልማት ዘላቂና አካታች ለማድረግ ዲጂታል መሰረተ ልማት ዝርጋታ ላይ ትኩረት በማድረግ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቅሰዋል። 2 1.1K
Обсуждение 0
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram